1998
From Wikipedia, the free encyclopedia
1998 አመተ ምኅረት
- መስከረም 18 ቀን - በሶማሊላንድ የምክር ቤት ምርጫ ተደርጎ የኡዱብ ፓርቲ አሸነፈ።
- መስከረም 27 ቀን - የፓላው ዋና ከተማ ከኮሮር ወደ መለከዖክ ተዛወረ።
- ኅዳር 13 ቀን - በጀርመን ፌዴራላዊ ሪፑብሊክ፣ አንጌላ መርክል የአገሪቷ የመጀመሪያዋ ሴት ርዕሰ መንግሥት (Chancellor) በመሆን የመሀላ ስርዐት ፈጽመው ሥልጣን ተቀበሉ።
- ኅዳር 14 ቀን - የአፍሪቃ አኅጉር የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚደንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ የላይቤሪያ መሪ ሆኑ።
- ኅዳር 21 ቀን - በካምፓላ ኡጋንዳ የተወለዱት ጆን ታከር ሙጋቢ ሴንታሙ ዘጠና ሰባተኛው የዮርክ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ። በዚህ ቤተ ክርስቲያን ይሄንን ታላቅ ሥልጣን የተቀበሉት የመጀመሪያው ጥቁር ጳጳስ ናቸው።
- መጋቢት 17 ቀን - የምየንማ መንግሥት በያንጎን ፈንታ ኔፕዪዶ አዲሱ ዋና ከተማ መሆኑን አዋጀ።
- ግንቦት 26 ቀን - ሞንቴኔግሮ ከሰርቢያ ተለየ።
- ሐምሌ 30 ቀን - ኢትዮጵያ፦ የደጫቱ ወንዝ ጎርፍ ከ200 በላይ የሆኑ ስዎችን ሕይወት አጠፋ።
- ያልተወሰነ ቀን -
- ግንቦት - ሳይበር-ኢትዮጵያ እንደሚለው፥ የኢትዮጵያ መንግሥት በፖለቲካዊ ምክንያት ዋርካ (ድረገጽ) ስለአገደው በኢትዮጵያ ውስጥ ሊታይ አልተቻለም።