ማርኮ ፖሎ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ማርኮ ፖሎ (1254 - ጥር 8፣ 1324) ጥንታዊው የጣሊያን ተጓዥ እና ነጋዴ ነበር። ታዋቂነትም ያተረፈው በተለይ ወደቻይና እና ሞንጎሊያ ከተጓዙት አውሮጳውያን ቀደምትነት ስለነበረው ነው። በዚህ ምክንያት ከሱ በኋላ ዘግይተው የተነሱት እነ ክርስቶፎር ኮሎምበስ ሳይቀር ለሱ ከፍተኛ ግምት እና አድንቆት እንደነበራቸው ታሪክ ይዘክራል። ት 1 17 አመት ሲሞላው ከጣሊያን ቬኒስ ከተማ በመነሳት፣ መጀመሪያ በጀልባ ከዚያም በእግሩና በግመል ተራሮችን በርሃን አቆራርጦ ቤይቺንግ ቻይና (በድሮ ስሟ ካቴ]) ለመድረስ ችሏል። በጊዜው ቻይና ትመራ የነበረው በሞንጎሉ መሪ ኩብላ ካህን የሚባለው የጌንጊዝ ካህን ልጅ ነበር። ስርዓቱም የዩዋን ሥርወ መንግስት ይባል ነበር። ለሚቀጥሉት 17 ዓመታት በኩብላ ካህን ቤተመንግስት አስተዳደር ተሰጥቶት መንግስቱን አገልግሏል። ከዚያም ወደ ጣሊያን በውቅያኖሶች አቋርጦ ተመልሷል። ወደ600 የሚሆኑ አብሮ ተጓዦች ግን በበሽታና በጥቃት ሞተዋል።
ይህ ተጎዥ ኑድል የተባለውን የቻይኖች የምግብ አይነት ወደ አገሩ ጣልያን በማምጣት የፓስታ ስራ አሰራርን ለጣሊያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋውቋል።
በጣሊያኖች እርስ በርስ ጦርነት ተማርኮ እስር ቤት ከገባ በኋላ ለእስር ጓደኛው ርስቲቸሎ የነገረውን ታሪክ ረስቲቸሎ ጽፎ በማሳተም ለማርኮ ፖሎ በአውሮጳ ዙርያ ታላቅ መታወቅን አስገኝቶለታል።