ኢሳያስ አፈወርቂ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ኢሳያስ አፈወርቅ (እኤአ ፌብራሪ 2፣1946 የተወለዱ) ፖለቲከኛ እና የኤርትራ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ፣ ለ30 ዓመት የዘለቀው እና የኤርትራ የነጻነት ትግል እየተባለ የሚጠራው ጦርነት ተጠናቆ የኤርትራ ሀገረ መንግስት ከትቋቋመ እኤአ ክ1991 ዓም ጀምሮ እስክ አሁን የኤርትራ መንግስት ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ። በተጨማሪም፣ ኢሳያስ አፈወርቅ መጀመሪያ የህዝባዊ ግንባር (ሻዕብያ) መሪ፣ በኋላም ህዝባዊ ግንባር ወደ ህግደፍ ሲቀየር የህግደፍ መሪ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
የዚህ መጣጥፍ የማያደላ ዝንባሌ ያለው ሁናቴ መኖሩ አጠያያቂ ጉዳይ ነው። (መግለጫውን በውይይት ገጽ ላይ ይፈልጉ።) |
==
ኢሳያስ አፈወርቅ | |
---|---|
አቶ ኢሳያስ እኤአ በ2022 የተነሱት | |
ባለቤት | ሳባ |
ልጆች | 3 ልጆች አብርሃም ኢሳያስ ኤልሳ ኢሳያስ ብርሃኔ ኢሳያስ |
የተወለዱት | አስመራ፣ ኤርትራ |
ፊርማ |
==
በኤርትራ ህገመንግስት፣ ምርጫ፣ ህግ አውጭ፣ እንዲሁም የሚታወቅ በጀት የሌለ ሲሆን፣ የህግ አስፈጻሚው፣ ወታድራዊወ፣ እንዲሁም የህግ አውጪው ስልጣን በፕሬዝዳንቱ ቁጥጥር ስር ይገኛሉ። ይህም በመሆኑ የተነሳ፣ አንዳንድ የአካዳሚክ ምሁራን እና የታሪክ አዋቂዎች አቶ ኢሳያስን እና መንግስታቸውን ፈላጭ ቆራጭ መንግስት እና አንባገነን እያሉ ይጠሯቸዋል። በተጨማሪም፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ደግሞ በሃገሪቱ ያለው የአገራዊ አገልግሎት በአስገዳጅነት የሚፈይፀም የጉልበት ብዝበዛ ነው በማለት በሰብአዊ መብት ጥሰት ይከሷቸዋል። እኤአ ሪፓርተርስ ዊዛውት ቦርደርስ፣ ኢሳያስ የሚመሯትነ ኤርትራ በጋዜጠኝነት ነጻነት ከ180 ሀገራት ውስጥ የመጨረሻዋ አድርጓታል።