ቅዱስ ጊዮርጊስ (ሰማዕት)
From Wikipedia, the free encyclopedia
ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ አንስጣቴዎስ (ዘሮንቶስ) ይባላል። እናቱም ቴዎብስታ ትባላለች የዘር ሐረግዋም ከፍልስጥኤም ወገን ነው ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ጥር ፪ ቀን ፪፻፸፯ ዓም ተወለደ የተወለደባትም ቦታ ቀጰዶቅያ ትባላለች።
ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት | |
---|---|
'በላሊበላ በቤተ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የሚገኝ የቅዱስ ጊዮርጊስ የግድግዳ ስዕል' | |
ታላቁ ሰማዕት | |
የተወለደው | ጥር ፪ ቀን ፪፻፸፯ ዓ.ም |
የአባት ስም | አንስታቴዎስ (ዘሮንጦስ) |
የእናት ስም | ቴዎብስታ |
የትውልድ ሀገር | ቀጰዶቂያ |
በዓለ ንግሥ | ሚያዚያ ፳፫ ቀን [1] |
ሃይማኖት | ክርስትና |
የሚከበረው | በምሥራቅም በምዕራብም ቤተክርስቲያኖች ሥንክሳር |
ቀጰዶቅያም በትንሹ ምሥራቃዊ እስያ(እንደዛሬ አጠራር መካከለኛው ምሥራቅ)ትገኛለች ከሮም ገናና መንግሥት በፊት በፋርስ መንግሥት ሥር ነበረች ። ጊዮርጊስም የፋርስ ሰማዕት የሚባለው በዚህ ምክኒያት እንደሆነ ይነገራል ይህችኑ ሀገር ግሪኮችና ሮማውያን በቀኝግዛት ይዘዋት እንደ ነበር ታሪክ ያብራራል ። በዚህ አኳኋን አንዳንድ ሰዎች ቅዱስ ጊዮርጊስን የግሪክ ተወላጅ ነው ሲሉ ሎችም ደግሞ የሮማ ተወላጅ ነው ይላሉ ጥቂቶችም የእንግሊዝ ዜጋ ነው ይላሉ ለዚህ ሁሉ ከአፈ ታሪክ በስተቀር ብዙ ጊዜ ተመራምሮ እስካሁን ድረስ በቂ ማስረጃ አልተገኘም። ከዚህም የተነሳ ጊዮርጊስ የዚህ ሀገር ተወላጅ የዚያኝው ሀገር ዜጋ ነው የሚል አነጋገር ቢሰጥ አያስደንቅም ምክኒያቱም የሥራ ሰውንና ጅግናን ማንም ሰው የሱ ዜጋ እንዲሆን ሰለሚፈልግ ነው ።
ይሁን እንጂ በዚያን ዘመን ወታደርነት ተፈላጊ ሙያ ስለነበር ቅዱስ ጊዮርጊስም ወታደር ሆኖ ብዙ ጀብዱ ፈፅሟል በወጣትነቱም የውትድርናን ሥራ እንደሠራ በግሪክና በኮብትና በሶርያ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ተጽፏል ይልቁንም በመጽሐፈ ስንክሳርና በራሱ ገድል ተብራርቶ ይገኛል።ቅዱስ ጊዮርጊስ ለጥቂት ጊዜ በወታደርነት ከሠራ በኋላ የክርስቶስ ወታደር ሆኖ ቤተክርስቲያንን ያገለግል ጀመረ ። ከቅዱስ ጊዮርጊስ ድረገጾች አንዱ ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ Archived ዲሴምበር 6, 2019 at the Wayback Machine